#Transfer_News -ሪያል ማድሪዶች የክረምቱ የዝውውር መስኮት ኤዱዋርዶ ካማቪንጋን ለማስፈረም ፍላጎት አሳይተዋል።
-ሳኦል ኒጉዬዝ እንደተናገረው በቀጣይ 3 ቀናት የምቀላቀልበትን ክለብ አሲውቃለሁ ብሏል።
-የሪያል ማድሪድ ተጫዋቾች በተደረገላቸው የሰውነት አቋም ፍተሻ ከተጫዋቾቹ ጋሪዝ ቤል ከሁሉም በተሻለ ጥሩ አቋም ላይ እንደሚገኝ [El Chiringuito] ዘግቧል።
ዲያጎ ሲሞኔ ካለ ቶማስ ፓርቴይ የአትሌቲኮ ማድሪድን አማካይ ክፍል ለማዋቀር ከወዲሁ እየተሰናዳ ነው። ለናፖሊው ብራዚላዊ አማካይ አለን ዝውውር ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን ለሙንዶ ዲፖርቲቮው ማውሮ አራምባሪንም ለማስፈረም በመንቀሳቀስ ወደ አርሰናል ይዛወራል ተብሎ ለሚጠበቀው ጋናዊ አማካይ ምትክ በማድረግ ሊያስፈርማቸው አስቧል።
ሪያል ማድሪድ በዚህ ሰአት ቢሸጡ ብዙ ብር ከሚያወጡ ክለቦች መካከል 1ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
የስፔኑ እግርኳስ ፕሬዝዳንት ጃቪዬር ቴባስ ለማርካ እንደተናገሩት የ2020/21 አመት ላሊጋ የሚጀመረው በፈረንጆቹ መስከረም 12 ነው።